Saturday, December 17, 2011

የዋሽንግተን ዲሲ ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት አቡነ አብርሃምን ሸኝቶ አቡነ ፋኑኤል ሊቀበል ነው

  














·  በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሔድ ብዙዎ አዝነዋል።
·  አቡነ ፋኑኤል በመመደባው ተቃውሞው በየሥፍራዉ እየቀጠለ ነው።
·  አቡነ ፋኑኤልን ከሕዝብ ለማቀራረብ መሐል ሰፋሪው ቡድን ደፋ ቀና እያለ ነው።

(ኖላዊ ዘተዋሕዶ፤ታህሳስ 72004)-ላለፉት ስድስት ዓመታት የኒዉዮርክ እና አካባቢው እንዲሁም የዋሽንግተን ዲሲ እና  አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወደ አዲሱ ሀገረ ስብከታቸው ወደ ሐረር ለመሄድ በዝግጅት ላይ ናቸው።ለብፁፅነታው ሽኝት መርሐ ግብር ለማዘጋጀት በሀገረ ስብከታቸው ሥር የሚገኙ ወጣቶች እና ካህናት እየተሰናዱ ነው።እንደ ብዙዎች እምነት ብፁዕነታቸው ከወጣቱ ጋር ተጋባብቶ በማስራትና በሃይማኖት ጉዳይ ጠንካራ  ነበሩ።ወቅቱ የተሐድሶ እንቅስቃሴ የተስፋፋበት ቤተ ከርስቲያን ከባድ ፈተና ላይ ያለበችበት እንደመሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃምን የመሰለ አባት ማጣት እጅጉን እንደሚከብድ አብዛኛው ወጣት በሀዘን ይገልጻል።

የአዲሱ ሚካኤል ምእመናን አስተዳዳሪው አባ ዕዝራ እንዲነሱ እየጠየቁ ነው

· ምእመኑ በየተራ ቤተክርስቲያኒቱን ሲጠብቅ ነው የሚያድረው
· አቤተታቸውን ለፓትርያርኩ አቀረቡ
· ፓትርያርኩ አጣሪ ኮሚቴ ይሾማል ብለዋቸዋል
(ኖላዊ ዘተዋሕዶ፤ታህሳስ 7 2004)- ቀደም ሲል በቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ላይ ምዝበራን ሲያካሂዱ በመገኘታቸው እንዲነሱ የተደረጉት  አባ ዕዝራ ተክለ ጊዮርጊስ  አሁን ደግሞ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል (አዲሱ ሚካኤል) ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሆነው ከተሾሙ በኋላ ቤተክርስቲያኒቱን  እየመዘበሩ እና ከአንድ መንፈሳዊ አባት የማይጠበቅ ተግባር እየፈጸሙ ነው በሚል ከአጥቢያው ምእመናን፣ከአጥቢያ መንፈሳዊ ማኅበራት እና ከደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተቃውሞ ገጠማቸው፡፡
በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን ጠቅላይ ቤተክህነት ለአቤቱታ ሄደው አቡነ ጳውሎስን ለማነጋገር ተስኗቸው ተመለሱ ሲሆን አምስት ሰው ብቻ ወክለው እንዲልኩ ተነግሯቸው ከላኩ በኋላ፣‹‹አጣሪ ኮሚቴ ይሾማል›› መባላቸውን ምጮች ጠቁመዋል አቤቱታ አቅራቢዎቹ ግን የአባ ዕዝራን እንዲነሱላቸው እንጂ አጣሪ ኮሚቴ እንደማይፈለጉ መናገራቸው ተሰምቷል፡፡በቤተክርስቲያኒቱ ተገኝተን ለማየት እንደሞከርነው፤በርካታ ምእመናን ‹‹መፍትሄ እስካልተሰጠን ድረስ አባ እዝራ ወደ ቤተክርስቲያኒቱ ገብተው ቢሮው ተጠቅመው ሕገወት ሥራ ሊሩ አይገባል በሚል››ተፈራርመው ቢሮውን ያሸጉት ሲሆን፡፡እርሳቸው ተነስተው መንፋሳዊ አባት እንዲሾምላቸውም 156 ገጽ ያለው የስምንት ሺህ ሰው ፊርማ ያለበት ሰነድ
ተመልክተናል፡፡

Sunday, December 11, 2011

የ“ሰባት ወይራ ሆቴል”ን አስመልክቶ ክስ የቀረበለት ፍርድ ቤት የቅዱስ ላሊበላ ደብር በባለቤትነት እንዲቆጣጠረው ወሰነ

 
      ·    የመንበረ ፓትርያርክ //ቤት አይመለከተውም ተብሎ ተሰናብቷል
·     የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደር ልማት ድርጅቱ እና ተከራዮቹ ከሆቴሉ ዞር እንዲሉ ተነግሯቸዋል   
·    ፓትርያርኩን አስተዳዳሪው ቆሞስ አባ ገብረ ኢየሱስ አሜሪካ ጉዞ  ጥርጣሬ ላይ ጥሏቸዋል
·     በአስተዳዳሪው ቆሞስ አባ ገብረ ኢየሱስ ላይ መዛታቸውም ተሰምቷል፡፡
·     ደብሩ ተከራዮቹን አስወጥቶ ሆቴሉን ተረክቧል
(ኖላዊ ዘተዋሕዶ፤ታህሳስ 1 2004)- የግርማዊ ቀዳማዊ ዐጼ ኀይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ የሆኑት ልዕልት ኂሩት ደስታ“ለቅዱስ ላሊበላ ደብር መርጃ ይሁን” በሚል በስጦታ ያበረከቱት የ‹‹ሰባት ወይራ ሆቴል ባለቤት››የቅዱስ ላሊበላ ደብር  መሆኑ በፍርድ ቤት ተረጋገጠ፡፡

የጉዳዩ መነሻ
የግርማዊ ቀዳማዊ ዐጼ ኀይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ የሆኑት ልዕልት ኂሩት ደስታ  በ1963 ዓ.ም “ለቅዱስ ላሊበላ ደብር መርጃ ይሁን” በማለት ደብሩ ሆቴሉን በባለቤትነት ይዞ እያስተዳደረ ገቢው ለማስቀደሻ እና ለጧፍ እንዲጠቀምበት በማሰብ የ‹‹ሰባት ወይራ ሆቴል››ን በጹሑፍ ይሰጣሉ፡፡ ገዳሙ ስጦታውን ከተቀበለ አራት ድፍን ዓመታት እንኳን በቅጡ ሳይቆጠር በደርግ የሥልጣን ዘመን ከተወረሱት በርካታ ቤቶች መካከል አንዱ ሆነና በጊዮን ሆቴሎች አስተዳደር ድርጅት እጅ ወደቀ፡፡ኢሕአዴግ የመንግሥትነቱን ሥልጣን ከተረከበ በኋላ 1991 . ፕራይቬታይዜሽን  ኤጀንሲ ለጠቅላይ ቤተክነት ‹‹ሰባት ወይራ›› የተባለው ሆቴል ንብረትነቱ የቅዱስ ላሊበላ ገዳም መሆኑ ስለተረጋገጠ፣ እንዲረከቡ የሚጠይቅ ደብዳቤ ይጽፋል፡፡ቤተክህነቱም ደብዳቤውን መነሻ በማድረግ ገዳሙ ሆቴሉን ለመረከብ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ ለደብሩ በደብዳቤ ያስታውቃል፡፡እነዚህ ደብዳቤዎች ከተጻጻፉ ከሰባት ዓመት በኋላ፣ 1997 .  ከገዳሙ እውቅና ውጪ በግዮን ሆቴሎች እና በጠቅላይ መካከል ርክክብ ይፈጸማል፡፡
ቤተክህነቱ
የገዳሙን የሰበካ ጉባኤ /ቤት ሆቴሉ ለገዳሙ የተበረከተ ስጦታ መሆኑን በመግለጽ ሆቴሉ ለደብሩ እንዲመለስ ቢጠይቁም ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሆቴሉን እንደ ሌሎቹ የተወረሱ የቤተክርስቲያኒቱ ቤቶች ከመንግሥት ጋር በተደረገ ልዩ ስምምነት ያስመለሰችው በመሆኑ፣ ንብረትነቱ የእርሷ እንጂ የገዳሙ ሊሆን እንደማይገባ በመግለጽ ሆቴሉም መተዳደር ያለበት በጠቅላይ ቤተክህነቱ ሥር ነው ስትል ክርክር ታቀርባለች፡፡በዚህም መሰረት በጠቅላይ ቤተ ክህነት የቤቶችና ሕንጻዎች አስመላሽ ኮሚቴ ከፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ተረክቦ ለሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት፣ ሀገረ ስብከቱም ለደብሩ ሊሰጥ ስምምነት ተደርሶ ነበር፡፡

Thursday, December 8, 2011

ያለጥናት የተጀመረው የአክሱም ሙዚየም ግንባታ ወጪ ፓትርያርኩን ለልመና ዳርጓቸዋል

·ከአክሱም ጉዟቸው በፊት 11 ሚሊዮን ብር ከየደብሩ እንዲሰጣቸው ጠይቀው ነበር
  (ኖላዊ ዘተዋሕዶሕዳር 28 2004)በአንድ ወቅት አዲስ አበባ የሚገኘውን ጊዮን ሆቴል ሊገዙ እንደሆነ የተነገረላቸው የግርማዊ ቀዳማዊ ዐጼ ኃይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ  እንደሚሠሩት ስለገለጹላቸው  ብቻ  ከማንም ጋር ሳይመካከሩ 350 ሚሊዮን ብር በሚደርስ ከፍተኛ ወጪ እንዲሠራ በአክሱም ከተማ ያስጀመሩት ሙዚየም ግንባታ ሁለተኛ ክፍያ ፤የአዲስ አበባ አድባራት እና ገዳማት፣ የአዲስ አበባ አገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች ከየትም ብለው አፈላልገው እንዲሰጡ ለሓላፊዎች ተነገራቸው፡፡ አድባራቱ የሚፈለግባቸውን 20 በመቶ ገቢ እንዲያስገቡ ተጠይቀዋል፡፡ የአዲስ አበባ አገረ ስብከት በክፍለ ከተሞች ልክ በ10  ተከፍሎ ይተዳደራል ተብሏል፡፡

ምንጮች እንደጠቆሙት፤ የግርማዊ ቀዳማዊ ዐጼ ኃይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ ሙዚየሙን ለመሥራት ቃል ከገባ እና ፓትርያርኩም ግንባታው ከ8 እስከ 9 ሚሊዮን ዩሮ እንዲሰራ ያለ ጨረታ ለተክለብርሃን አምባዬ  ኮንስትራክሽን ከሰጡ በኋላ ቃል የገባው ግለሰብ ሊያገኙት እንዳልቻሉ ነው፡፡ ፓትርያርኩ በስሜት ተነሳስተው ጥናት ላልተደረገበት ፕሮጀክት 16 ሚሊዮን ብር ቅድሚያ ክፍያ የከፈሉ ሲሆን ኮንትራክተሩ ሁለተኛው ክፍያ እንዲከፈለው አስጨንቆ እንደያዛቸው ሲናገሩ ተሰምተዋል፡፡

Tuesday, December 6, 2011

ኖላዊ  ዘተዋሕዶ  ማን ነዉ?
                              
                                           ኖላዊ  ዘተዋሕዶ 
ኖላዊ  ዘተዋሕዶ ማለት የተዋሕዶ እረኛ ማለት ነው።ተዋሕዶ ሃይማኖት እረኛዋ ጠባቂዋ ቤዛ ኲሉ ዓለም ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ተዋሕዶ ሃይማኖት ነቅዕ ንጹሕ (የጠራ ምንጭ) ናት።ከጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቶቻችን ሐዋርያት ኋላም ለሊቃውንት ቀጥሎም ለካህናት በአደራ የተሠጠች አንዲት ሃይማኖት ናት/ ይሁ 1-3//ኤፌ4-5/።የቅዱሳን ርስት፣የባህታውያን የጸሎት ፍሬ፣የሰማዕታት ተጋድሎ፣የምእመናን ተስፋ ናት።ስለዚህም በልዑል እግዚአብሔር ታላቅ ቸርነት የዚህች ርትዕት ሃይማኖት ልጆች በመሆናችን አንደበታችን ሁልጊዜም ፈጣሪን ያመሰግናል።
ዘመናችን ሰይጣን የሰው ልጆችን ሕይወት እንደ ስንዴ ለማበጠር በውስጥ በአፍአ ፈተና ያበዛበት ዘመን ነው/ሉቃ 22-31/። ይህችህን ቅድስት ሃይማኖት ለማወክ ማዕበል በየአቅጣጫው አስነስቶ የምናይበት ነው።እንዲህ  ባለው የፈተና ወቅት ማንቀላፋት ተገቢ እንዳልሆነ እናምናለን።በመንፈሳዊ ሕይወታችን ከሌላው የተሻልን እንደሆንን ራሳችንን ባንቆጥርም በቤተክርስቲያኒቱ ላይ እየደረሰው ያለው ሁኔታ ግን ያሳስበናል።አይተን እንዳላየን እንዳንሆንም የቅዱሳን አበው የአደራ ቃል ግድ ይለናል።